• +251115526653
  • info@etsugar.com
  • Phillips Building, Chad St, Addis Ababa, Ethiopia
ግሩፑ ማዕድ አጋራ

ግሩፑ ማዕድ አጋራ

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለሚገኙ አቅመ ደካሞች ማዕድ አጋራ፡፡የ2016 አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በተከናወነ የማዕድ ማጋራት ሥነ ሥርዓት በወረዳው ለሚገኙ አቅመ ደካሞች ዱቄትና ዘይት ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይና በአስር ዓመቱ አገራዊ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ

በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይና በአስር ዓመቱ አገራዊ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት አመራር አባላትና ሠራተኞች በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይና በአስር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ላይ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አድርገዋል፡፡

የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማትና የአርብቶ አደሩ ተጠቃሚነት በከፊል

የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማትና የአርብቶ አደሩ ተጠቃሚነት በከፊል

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ለአካባቢው ማሕበረሰብ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን የመሠረት ልማት ማለትም መንገድ፣ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ የእንስሳት ጤና ኬላዎች እንዲሁም ለእንስሳት መሻገሪያነት የሚያገለግሉ የድልድይ ግንባታዎችን አከናውኗል፡፡

የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ከሐምሌ ወር ጀምሮ ስኳር እያመረተ ይገኛል

የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ከሐምሌ ወር ጀምሮ ስኳር እያመረተ ይገኛል

የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የሁለተኛ ምዕራፍ የምርት ወቅቱን ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም በመጀመር ስኳር እያመረተ ይገኛል፡፡
በቀን በአማካይ 3ሺህ ኩንታል ስኳር በማምረት ሂደት ላይ የሚገኘውን የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ አቅም በማሳደግ በሂደት በቀን በአማካይ እስከ 5 ሺህ ኩንታል ስኳር እንዲያመርት የሚያስችል የአገዳ አቅርቦት የማስፋፋት ሥራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ፋብሪካው እስከ መስከረም ወር 2016 ዓ.ም አጋማሽ ድረስ በምርት ላይ የሚቆይ ሲሆን በዚህ የፋብሪካው የሁለተኛው ምዕራፍ የምርት ወቅትም እስከ 150 ሺህ ኩንታል ስኳር ይመረታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ 
ፋብሪካው በመጀመሪያው ምዕራፍ የምርት ወቅት 203 ሺህ 218.5 ኩንታል ስኳር አምርቷል፡፡
የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 እና ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካዎች ከሚገኙበት አካባቢ የአየር ንብረት ጋር በተያያዘ በዓመት ውስጥ ሁለት የምርት ወቅቶች አሏቸው፡፡

የተቋሙን ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ወጪ መቆጠብና ብክነትን ማስወገድ እንደሚገባ ተገለጸ

የተቋሙን ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ወጪ መቆጠብና ብክነትን ማስወገድ እንደሚገባ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የጀመራቸውን ተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ወጪ መቆጠብ እና ብክነት ማስወገድ ላይ አመራሩና ሠራተኛው ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ፡፡ የግሩፑ የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2016 ዕቅድ ላይ የዋና መስሪያ ቤት አመራር አባላትና ሠራተኞች የተሳተፉበት ውይይት በቢሾፍቱ ተደርጓል፡፡

የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክቶችና ፋብሪካ የ2015 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ግምገማ ተካሄደ

የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክቶችና ፋብሪካ የ2015 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የ2016 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ግምገማ ተካሄደ

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ከፍተኛ የማኔጅመንት አባላትና የግሩፑ የሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክቶችና ፋብሪካ በመገኘት የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን፣ የፕሮጀክቶች የሥራ እንቅስቃሴን እና የ2016 ምርት ዘመን ዕቅድን ገመገሙ፡፡

የስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አመራር አባላትና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አከናወኑ

የስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አመራር አባላትና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አከናወኑ

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አመራር አባላት እና ሠራተኞች በዘንድሮው ዓመት “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ የተያዘውን የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ተግባራዊ ለማድረግ ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ገላን ኮንዶሚኒዬም አካባቢ በመገኘት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሄዱ፡፡